በዓለ-ንግሥ አከባበር ሥነ ሥርዓት በደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም

ከዚህ በታች በቪዲዮ ይመልከቱ፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በዝዋይ ገዳም በመሰራት ላይ ያለውን የቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ጎበኙ፡፡ እንደዚሁም የ3ወር ሰልጣኝ ደቀ መዛሙርትን መርቀዋል፡፡

ከዚህ በታች በቪዲዮ ይመልከቱ፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የግብፅ የህክምና ባለሙያዎችን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በተለያዩ ሀገራት በከፍተኛ በህክምና ሥራ ላይ ተሰማርተው የሚሠሩ የግብጽ የህክምና ባለሙያዎችን ተቀብለው በጽ/ቤታቸው አነጋግረዋል፡፡

ለተጨማሪ ንባብ እዚህ ይጫኑ፡፡

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት-ዘትንሣኤ

በትንሣኤው ትንሣኤያችንን ያበሰረን ጌታችን አምላካችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለ2005 ዓ.ም. በዐለ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ለተጨማሪ ንባብ እዚህ ይጫኑ፡፡ ወይም ከዚህ በታች በቪዲዮ ይመልከቱ፡፡

የትንሳኤ በዓል አከባበር በቤተ ክህነት አዳራሽና በሰበታ ቤተ ደናግል ገዳም

በቤተ ክህነት አዳራሽ
በሰበታ ቤተ ደናግል ገዳም

የዕለተ ስቅለት-ዓርብ ሥርዓተ ጸሎትና ስግደት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አራት ኪሎ

የጸሎተ ሐሙስ ሥርዓት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አራት ኪሎ

የሆሳዕና በዓል አከባበር አና የሙዝየም ጉብኝት በአክሱም ጽዮን

ሆሳዕና በዓል አከባበር
የሙዝየም ጉብኝት በአክሱም ጽዮን

እንኳን ለጌታችን፣ ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የ2ዐዐ5 ዓ.ም. መዋዕለ ጾም በሰላም አደረሳችሁ፡፡

"እብለክሙ በመንፈስ ሑሩ፤ ወፍትወተ ሥጋክሙ ኢትግበሩ" ‹በመንፈስ ተመላለሱ እንጂ የሥጋችሁን ምኞት ከቶ አትፈጽሙ እላችኋለሁ› (ገላ. 516)

የሰው ልጅ ከዐራቱ ባሕርያተ ሥጋ ከሦስቱ ባሕርያተ ነፍስ የተገኘ ፍጡር እንደመሆኑ በሥጋዊ ፍላጎቱ ሳይሸነፍ ራሱን ለመንፈሳዊ ሕይወቱ ማስገዛት እንዳለበት መጽሐፈ ቅዱስ ያስረዳናል ፡፡ ከዚህም አንፃር "በመንፈስ ተመላለሱ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በሥጋ ላይ ይመኛልና" ይላል የእግዚአብሔር ቃል ፡፡ ለተጨማሪ ንባብ እዚህ ይጫኑ፡፡ ወይም ከዚህ በታች በቪዲዮ ይመልከቱ፡፡

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ሲመት

ራሱን ቅዱስ ሲኖዶስ ብሎ የሚጠራው አካል ያወጣውን የሐሰት መግለጫ በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

ስሕተት በባህርዩ ጉጂና በማናቸውም ጊዜ የማይደገፍ ቢሆንም ከሰው ጋር አብሮ የሚኖር በመሆኑ ሰው ከስሕተት ጸድቶ አያውቅም፤ ስሕተትም ከሰው ጠፍቶ አያውቅም፡፡

ለተጨማሪ ንባብ ቁጥር 1 ን እና 2 ን በመጫን ያንብቡ፡፡

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ6ኛው ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የተቋቋመው የ6ኛው ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ የምርጫውን ሂደት በተመለከተ ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም አጠቃላይ መግለጫ መስጠቱ ይታወሳል ፡፡ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫም የሚዲያ ተቋማት መልዕክቱን ለህዝብ እንዲደርስ ስላደረጋችሁ በቤተክርስቲያናችን ስም እናመሰግናለን ፡፡

ሙሉውን መግለጫ እዚህ በመጫን ያንብቡ፡፡

ስድስተኛውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ለማስመረጥ ከተቋቋመው አስመራጭ ኮሚቴ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በራሷ ሲኖዶስ መመራት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በብፁአን ሊቃነ ጳጳሳት፣ በካህናትና በምዕመናን፣ በሰንበት ት/ቤት ወጣቶች አምስት ቅዱሳን ፓትርያርኮችን እየመረጠች በመንበራቸው አስቀምጣለች፡፡ ባለፉት በርካታ ዓመታት የተመረጡት ቅዱሳን ፓትርያርኮችም ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና ለሀገራችን ለኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን አከናውነዋል፡፡

ሙሉውን መግለጫ እዚህ በመጫን ያንብቡ፡፡

ወደ ገፅ 1 2 3 >>